አንኳሮች
- የነባር ዜጎች ድምፅ ላፓርላማ ሕዝበ ውሳኔ ውጤት ከዳር እስከ ዳር 'አይሁን' ሆኗል
- ስድስቱ ክፍለ አገራትና ሰሜናዊ ግዛት 'አይሁን' ሲሉ፤ የአውስትራሊያ መዲና ግዛት 'ይሁን' ብላለች
- ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኒዚ አውስትራሊያውያን ወደ አንድነት እንዲመለሱ አበረታተዋል
አውስትራሊያውያን የነባር ዜጎች ድምፅ ለፓርላማ በሕገ መንግስቱ ውስጥ እንዳይሰፍር ውድቅ አድርገዋል።
'አይሁን' የሚለው ድምፅ ቅዳሜ በተካሔደው ታሪካዊ ሕዝበ ውሳኔ ወቅት በሁሉም ስድስት ክፍለ አገራትና ሰሜናዊ ግዛት ተመዝግቧል።
የ'አይሁን ' ድምፅ በብሔራዊ ደረጃ የተመዘገበው አብላጫ ድምፅ በመያዝ ነው።

Ballot papers are seen at a counting centre in Melbourne, Saturday, October 14, 2023. Australians will vote in a referendum on October 14 on whether to enshrine an Indigenous voice in the country's constitution. (AAP Image/Con Chronis) NO ARCHIVING Source: AAP / CON CHRONIS/AAPIMAGE
ከመላ አገሪቱ የአስተዳደር አካላት 'ይሁን' የሚለው ድምፅ የተመዘገበው በአውስትራሊያ መዲና ግዛት ብቻ ነው።
በቅሬታ የዋጡት ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልበኒዚ ውጤቱ "ለይቶ አይገልጠንም፤ እንዲሁም አይለያየንም"
"ከእዚህ በኋላ መሰባሰቡና ተመሳሳይ የታረቀ መዳረሻ ላይ ለመድረስ የተለየ መንገድ መፈለግ የእኛ የሁላችን ፈንታ ነው" በማለት አበክረው ተናግረዋል።

Australian Prime Minister Anthony Albanese delivers a statement on the outcome of the Voice Referendum at Parliament House.
"የጥያቄ አቅርቦቱና ሂደቱ አውስትራሊያውያንን በኅብረት ለማቆም እንጂ፤ ሊከፋፍለን መሆን አልነበረበትም" ብለዋል።

Opposition Leader Peter Dutton and Shadow Minister for Indigenous Australians Senator Jacinta Price address the media following the referendum. Source: AAP / JONO SEARLE/AAPIMAGE
የ 'ይሁን' አቋም አራማጇ የነባር ዜጎች ሚኒስትር ሊንዳ በርኒ ሕዝበ ውሳኔውን ተከትሎ የአዲሱ ትውልድ ነባር ዜጎች መሪዎች ብቅ እንደሚሉ አመኔታቸውን ገልጠዋል።
ውጤቱ የሚያመለክተው ነባር ዜጎች ምንም ዓይነት ዕክሎች ይግጠማቸው፤ አውስትራሊያውያን "የሚሹት ነገሮች እንዲከወኑ" ያመላከቱት ሁነኛ የ 'አይሁን' ዘመቻ አካሔጁ ኑንጋይ ዋረን ማንዲን፤
"ሰዎች የተወሰኑ ነባር ዜጎች ማኅበረሰባት ውስጥ የሚከሰቱ አመፅ፣ ማጎሳቆል፣ አስገዳጅ ቁጥጥርና ጎጂ ባሕሪይን አስመልክቶ ዓይን ጭፈናቸውን ማቆም አለባቸው" ብለዋል።
በ NITV የሚተላልፈውን የነባር ዜጎች አተያዮችን አስመልክቶ የ2023 ድምፅ ለፓርላማን በተመለከተ በመላው SBS አውታረ መረብ ይከታተሉ።
ከ60 በላይ ከሆኑ ቋናቋዎች ውስጥ መጣጥፎችን ለማንበብ፣ ቪዲዮዎችን ለመመልከትና ፖድካስቶችን ለማድመጥ ይጎብኙ፤ ወይም የቀጥታ ዜናዎችንና ትንታኔዎችን፣ ዘጋቢ ፊልሞችንና መዝናኛዎችን በነፃ ለመከታተል ይጎብኙ።