የነባር ዜጎች ድምፅ ለፓርላማ ዳር እስከ ዳር እምቢታ ገጠመው

R2R.jpg

The Aboriginal flag and Torres Strait Islanders flags. Credit: SBS

አውስትራሊያውያን የነባር ዜጎች ድምፅ ለፓርላማ በሕገ መንግሥቱ እንዳይካተት ሰሜናዊ ግዛትን አክሎ በስድስቱም ክፍለ አገራት በ 'አይሁን' ድምፅ ውድቅ አድርገውታል።


አንኳሮች
  • የነባር ዜጎች ድምፅ ላፓርላማ ሕዝበ ውሳኔ ውጤት ከዳር እስከ ዳር 'አይሁን' ሆኗል
  • ስድስቱ ክፍለ አገራትና ሰሜናዊ ግዛት 'አይሁን' ሲሉ፤ የአውስትራሊያ መዲና ግዛት 'ይሁን' ብላለች
  • ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኒዚ አውስትራሊያውያን ወደ አንድነት እንዲመለሱ አበረታተዋል
አውስትራሊያውያን የነባር ዜጎች ድምፅ ለፓርላማ በሕገ መንግስቱ ውስጥ እንዳይሰፍር ውድቅ አድርገዋል።

'አይሁን' የሚለው ድምፅ ቅዳሜ በተካሔደው ታሪካዊ ሕዝበ ውሳኔ ወቅት በሁሉም ስድስት ክፍለ አገራትና ሰሜናዊ ግዛት ተመዝግቧል።

የ'አይሁን ' ድምፅ በብሔራዊ ደረጃ የተመዘገበው አብላጫ ድምፅ በመያዝ ነው።
VOICE REFERENDUM COUNTING
Ballot papers are seen at a counting centre in Melbourne, Saturday, October 14, 2023. Australians will vote in a referendum on October 14 on whether to enshrine an Indigenous voice in the country's constitution. (AAP Image/Con Chronis) NO ARCHIVING Source: AAP / CON CHRONIS/AAPIMAGE

ከመላ አገሪቱ የአስተዳደር አካላት 'ይሁን' የሚለው ድምፅ የተመዘገበው በአውስትራሊያ መዲና ግዛት ብቻ ነው።

በቅሬታ የዋጡት ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልበኒዚ ውጤቱ "ለይቶ አይገልጠንም፤ እንዲሁም አይለያየንም"

"ከእዚህ በኋላ መሰባሰቡና ተመሳሳይ የታረቀ መዳረሻ ላይ ለመድረስ የተለየ መንገድ መፈለግ የእኛ የሁላችን ፈንታ ነው" በማለት አበክረው ተናግረዋል።
PM Anthony Albanese .jpg
Australian Prime Minister Anthony Albanese delivers a statement on the outcome of the Voice Referendum at Parliament House.
የተቃዋሚ ቡድን መሪ ፒተር ዳተን የሕዝበ ውሳኔን ሂደት "አስፈላጊ ያልሆነ" ሲሉ ጠርተው፤ አገሪቱ በኅብረት እንድትቆም ጥሪ አቅርበዋል።

"የጥያቄ አቅርቦቱና ሂደቱ አውስትራሊያውያንን በኅብረት ለማቆም እንጂ፤ ሊከፋፍለን መሆን አልነበረበትም" ብለዋል።
PETER DUTTON VOICE REFERENDUM ADDRESS
Opposition Leader Peter Dutton and Shadow Minister for Indigenous Australians Senator Jacinta Price address the media following the referendum. Source: AAP / JONO SEARLE/AAPIMAGE
የተወሰኑ የአውስትራሊያ ነባር ዜጎች የሕዝበ ውሳኔውን ድምፅ ውጤት ተከትለው የአንድ "ሳምንት ፀጥታ" ሲመርጡ፤ ሌሎች ከወዲሁ ቀጥሎ ምን ማድረግ እንደሚገባ ማሰብ ጀምረዋል።
የ 'ይሁን' አቋም አራማጇ የነባር ዜጎች ሚኒስትር ሊንዳ በርኒ ሕዝበ ውሳኔውን ተከትሎ የአዲሱ ትውልድ ነባር ዜጎች መሪዎች ብቅ እንደሚሉ አመኔታቸውን ገልጠዋል።

ውጤቱ የሚያመለክተው ነባር ዜጎች ምንም ዓይነት ዕክሎች ይግጠማቸው፤ አውስትራሊያውያን "የሚሹት ነገሮች እንዲከወኑ" ያመላከቱት ሁነኛ የ 'አይሁን' ዘመቻ አካሔጁ ኑንጋይ ዋረን ማንዲን፤

"ሰዎች የተወሰኑ ነባር ዜጎች ማኅበረሰባት ውስጥ የሚከሰቱ አመፅ፣ ማጎሳቆል፣ አስገዳጅ ቁጥጥርና ጎጂ ባሕሪይን አስመልክቶ ዓይን ጭፈናቸውን ማቆም አለባቸው" ብለዋል።
በ NITV የሚተላልፈውን የነባር ዜጎች አተያዮችን አስመልክቶ የ2023 ድምፅ ለፓርላማን በተመለከተ በመላው SBS አውታረ መረብ ይከታተሉ።


ከ60 በላይ ከሆኑ ቋናቋዎች ውስጥ መጣጥፎችን ለማንበብ፣ ቪዲዮዎችን ለመመልከትና ፖድካስቶችን ለማድመጥ ይጎብኙ፤ ወይም የቀጥታ ዜናዎችንና ትንታኔዎችን፣ ዘጋቢ ፊልሞችንና መዝናኛዎችን በነፃ ለመከታተል ይጎብኙ።

Share