የኮቪድ - 19 ወቅታዊ መረጃ፤ የኒው ሳውዝ ዌይልስ ገጠራማ ከተማ ኮውራ የኮሮናቫይረስ ገደብ ተጣለባት

*** ቪክቶሪያ ውስጥ 4,800 አስትራዜኔካና ከ2,000 በላይ ፋይዘር ለተከታቢዎች ዝግጁ ናቸው

COVID-19 update

The regional town of Cowra in NSW. Source: Getty

  • ኮውራ ላይ  ከዛሬ 5pm ጀምሮ የኮሮናቫይረስ ገደብ ተጣለ
  • ቪክቶሪያ ውስጥ በሺህዎች የሚቆጠሩ ክትባቶች ለተከታቢዎች ዝግጁ ናቸው
  • የአውስትራሊያ ካፒታል ቴሪቶሪ ዕድሜያቸው ከ12-15 ላሉ የፋይዘር ክትባት ቀነ ቀጠሮ ማስያዝ ጀመረች
  • ኖርዘርን ቴሪቶሪ ውስጥ አንድ መንገደኛ በኮቪድ ተጠቃ

ኒው ሳውዝ ዌይልስ
ኒው ሳውዝ ዌይልስ 935 ነዋሪዎቿ በቫይረስ ተጠቁ። አራት ሰዎች ሕይወታቸውን አጡ። የክትባት መመዘኛዎችን ከሚያሟሉ ነዋሪዎች ውስጥ 52.7 ፐርሰንት ሙሉ ክትባት ተከትበዋል። 

ኮውራ ውስጥ አንድ የዘጠኝ ዓመት ልጅ ተያዘ። በርካታ የተጋላጭነት ሥፍራዎች ተመዘገቡ  የሪጂናል ከተማዋ ላይ ገደብ የሚጣለው ከዛሬ 5pm አንስቶ ነው።ከሴፕቴምበር 13 ጀምሮ ኮውራ የነበሩ ማናቸውም ሰዎች "የቤት ውስጥ ቆይታ መስፈርቶችን በአስቸኳይ እንዲተገብሩ" ማሳሳቢያ ተሰጥቷል። ከተማይቱ ውስጥ ቫይረሱ እንደምን እንደተከሰተ ለጊዜው አልታወቀም። 

የኒው ሳውዝ ዌይልስ ዳርቶን ከተማ የቁሻሻ ፍሳሽ ውስጥ የቫይረስ ምልክት በምርመራ ተገኝቷል።

ዛሬውኑ የክትባት ቀጠሮዎን ለማስያዝ ይህን ይጫኑ  

ቪክቶሪያ
ቪክቶሪያ በዛሬው ዕለት 567 ነዋሪዎቿ በኮሮናቫይረስ ተጠቅተዋል። የአንድ ሰው ሕይወት አልፏል።

እንደራሴ ዳንኤል አንድሩስ 4,800 አስትራዜኔካና ከ2,000 በላይ ፋይዘር ለተከታቢዎች ዝግጁ መሆኑን ገለጡ። በቂ የፋይዘር ክትባት ኦክቶበር ውስጥ ላይኖር እንደሚችል በማመልከት ሰዎች ለጊዜው ዝግጁ ሆኖ ያለውን የክትባት ዓይነት እንዲከተቡ አሳስበዋል።

አቅራቢያዎ የሚገኝ የክትባት ማዕከልን ማወቅ ካሹ ይህን ይጫኑ   

የአውስትራሊያ ካፒታል ቴሪቶሪ
የአውስትራሊያ ካፒታል ቴሪቶሪ ሰባት ነዋሪዎቿ በቫይረስ መያዛቸውን አስመዝግባለች። ዋና ሚኒስትር አንድሩ ባር 55 ፐርሰንት የአውስትራሊያ ካፒታል ቴሪቶሪ ነዋሪዎች የሁለተኛ ዙር ክትባቶችን መከተባቸውን አስታወቁ። 

ዕድሜያቸው ከ 12 እስከ 15 ያሉ ከዛሬ ጀምሮ በመንግሥት በሚካሄዱ ክሊኒኮች ዘንድ የክትባት ቀጠሮ ማስያዝ ይችላሉ። 

የኮቪድ-19  ክትባት ቀጠሮ ለማስያዝ ይህን ይጫኑ to                                                                                             

ያለፉት 24 ሰዓታት በአውስትራሊያ ዙሪያ
  • አንድ ከብሪስበን አውሮፕላን ማረፊያ ተነስቶ ኖርዘርን ቴሪቶሪ ያረፈ መንገደኛ በቫይረስ የተጠቃ ሆኖ ተገኝቷል።
 


Share
Published 20 September 2021 3:21pm
Updated 20 September 2021 3:28pm
By SBS/ALC Content
Presented by Kassahun Seboqa Negewo
Source: SBS

Share this with family and friends