የኮቪድ-19 የተሻሻለ መረጃ ፡ በኒው ሳውዝ ዊልስ የሟቾች ቁጥር እንደሚጨምር የሚጠብቅ ሲሆን በቪክቶሪያም ከፍተኛ የሚባልባት ደረጃ ለመድረስ ተቃርቧል

*** በኒው ሳውዝ ዌልስ 29,504 ሰዎች በቫይረሱ የተያዙ ሲሆን የ17 ሰዎች ህይወት አልፏል ። በቪክቶሪያ 22,429 ሰዎች በኮቪድ-19 ሲያዙ የስድስት ሰዎች ህይወትም አልፏል ።

Victorian Chief Health Officer Brett Sutton addresses the media during a press conference in Melbourne.

Victorian Chief Health Officer Brett Sutton addresses the media during a press conference in Melbourne. Source: AAP

    • በመጪዎቹ ቀናት በኒው ሳውዝ ዌልስ በኮቪድ- 19ሳቢያ የሟቾች ቁጥር እንደሚጨምር የሚጠበቅ ሲሆን ፤ ይህም የሚሆነው በማህበረሰብ መካከል በሚሰራጭ ቫይረስ አማካኝነት መሆኑን ከፍተኛ የጤና ኦፊሰሯ ኬሪ ቻንት አስጠንቅቀዋል ።
    • በኒው ሳውዝ ዌልስ ከቫይረሱ ጋር በተያያዘ 17 ሰዎች የሞቱ ሲሆን ፤ በተያያዥም በሆስፒታል እና ልዩ እንክብካቤ የሚስፈልጋቸው ሰዎች በሚታከሙበት ክፍል የሚቆዩ ሰዎች ቁጥር መጨመሩ ተገልጿል ።
    • ዶ / ር ቻንት እንደተናገሩት “ ተጨማሪ ማጠናከሪያ ክትባትን በመውሰድ ፤ መከላከያን ከፍ በማድረግ ኦሚኮርንን መከላከል ግድ ይላል ፤ በሪፖርታቸውም አያይዘው እንደገለጹት ባለፉት ሁለት ቀናት በግል የደም መስጫ ተቋም ከተሰበሰቡት ናሙናዎች መካከል 95 በመቶ የሚሆኑት የኦሚኮርን ቫርያንት ናቸው ።
    • የቪክቶሪያ ከፍተኛ የጤና ኦፊሰር ብሬት ሰተን ፤ ምንም እንኳ በማህበረሰቡ ውስጥ የተዛመተው ከፍተኛ ቁጥር ያለው የቫይረስ ስርጭት ሪፖርት ባይደረግም ፤ ከተማዋ በቅርቡ ሰርጭቱ “ ከፍተኛ ” ደረጃ የሚባልበት ላይ እንደምትደርስ ተናግረዋል ።
    • ከኩዊንስላንድ የተገኙት የቁጥር መረጃዎች እንደሚያመላክቱት ፤ አንድ ያልተከተበ ሰው ሶስቱንም ክትባቶች ከወሰዱት ጋር ሲነጻጸር ፤ ከፍተኛ እንክብካቤ የሚያሻቸው ህሙማን ክፍል ውስጥ የመቆየት እደሉ በ24 እጥፍ ከፍ ያለ ነው ።
    • የአውስትራሊያ ተጠቃሚዎች ተቆጣጣሪ እንዳለው የፈጣን መመርመሪ መሳሪያዎቹ ዋጋ በየጊዜው መናር አሳሳቢ መሆኑን ነው ።
    • የአውስትራሊያ ተጠቃሚዎች ተቆጣጣሪ ከ 1,800 በላይ አሀዛዊ ሪፖርቶችን የተነተነ ሲሆን ፤ የዋጋ መጨመር የታየው ካለፈው ዲሴምበር 25 ጀምሮ ሲሆን ፤ በአሁን ሰአትም ከ 150 በላይ ሪፖርቶች በየቀኑ ይወጣሉ ።
    • ቪክቶሪያ ክትባትን ለማበረታታት 1.2 ሚሊዮን ዶላር ለመድበለ ባህል የማህበረሰብ አባላት የመደበች ሲሆን ፤ ይህውም በስምንት የማህበረሰብ ድርጅቶች አማካኝነት የቋንቋ እርዳታን ለሚሹ ፤ በገበያ ማእከላት እና የክትባት ጣቢያዎች ክትባቱን ለማዳረስ የሚወል ይሆናል ።
    • የፌደራል መንግስት በጊዜያዊነት የሚያገለግል የልዩ ሀኪሞች ቴሌ ሄልዝ በስልክ እና ቪዲዮ አገልግሎት የሚያስተዋውቅ ሲሆን ፤ ይህውም የመጀመሪያ እና ውስብስብ ልዩ የስልክ ህክምናን ፣ ረጅም የቤተሰብ ሀኪም ማማከርን የሚያጠቃልል እና እስከ ጁን 30 የሚዘልቅ ነው ።
    • ኮቫክ ( COVAX )  የተባለው አለማቀፍ ድርጅት ክትባትን በመጋራት ዙሪያ አንድ ቢሊዮን ክትባቶችን ያዳረስ ቢሆንም ፤ እስከአሁንም ድረስ 40 በመቶ የሚሆነው የአለማችን ህብረተሰብ አልተከተበም ።
    የፈጣን ምርመራን ቅጽ ያዘጋጁ ክፍላት ሃገራት ዝርዝር ፦

    የኮቪድ - 19 ስታትስቲክስ

  • በኒው ሳውዝ ዌልስ 29,504 ሰዎች በቫይረሱ የተያዙ ሲሆን የ17 ሰዎች ህይወት አልፏል ። በቪክቶሪያ 22, 429 ሰዎች በኮቪድ-19 ሲያዙ የስድስት ሰዎች ህይወትም አልፏል ።

  • በኩዊንስላንድ 15,122 ስዎች ሲያዙ የ 7 ስዎች ህይወት አልፏል ። በታዝማንያ 1037 ሰዎች በቫይረሱ ተይዘዋል ።

  •  በአሁን ሰአት የኮቪድ-19 ወረርሽኝን ላይ እየተሰጠ ያለውን ምላሽ በተመለከተ በቋንቋዎ መረጃን ካሹ የሚከትለውን ሊንክ ይጫኑ .


ወሸባና ገደቦች ክፍለ አገር በክፍለ አገር ፤

ጉዞ

የአለማቀፍ ጉዞን በተመለከተ መረጃዎችን እና የ ኮቪድ-19 የጉዞ መረጃዎችን በቋንቋዎ ያግኙ

የአለማቀፍ ጉዞን በተመለከተ መረጃዎችን  እና የ ኮቪድ-19 የጉዞ መረጃዎችን በቋንቋዎ ያግኙ

የገንዘብ እርዳታ

በየክፍላት ሀገሩ ሙሉ ለሙሉ የተከተቡ ሰዎች ቁጥር ከ 70 እና 80 በላይ ከሆነ ጀምሮ የክፍለ ሀገሮች የኮቪድ-19 የአደጋ ጊዜ ክፍያ ህጎች ተለውጠዋል።:

 



በኒው ሳውዝ ሄልዝ መድብለባህል የጤና ክህለ ተግባቦት አገልግሎት የተተረጎሙ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን ሊንኮች ይጫኑ ፦


የየክፍላተ ሀገራቱ እና ግዛቶች የመመርመሪያ ክሊኒኮች ዝርዝር ፦

 
 

Share
Published 17 January 2022 4:18pm
Updated 17 January 2022 4:21pm
Presented by Martha Tsegaw


Share this with family and friends